Thursday, December 26, 2013

እኛና እነሱ /ዝቅ በል/ !

በአለም ላይ ካሉ ሃገሮች ውስጥ ስልጣን የሌለበት ሃገር ቢኖር ወይም ባለስልጣኑ ህዝብ የሆነበት ሃገር ቢኖር ሳላጋንን ኖርዎይ የምትባለው ሃገር ናት ማለት እችላለሁ፥፥ በግልፅ ህዝቡ የሚፈልገውን፥ ያስተዳድረኝ እገዛለታለሁ ብሎ አምኖ ድምፁን የሚሰጥለት መሪ፥፥ መሪውም ከልቡ እራሱን ዝቅ አርጎ ለሃገሩ፥ ለወገኑ የሚሰራበት ሃገር፥፣ ህገመንግስቱ ወይም በኖርዌጅያኑ አጠራር /GrunnLov/ ለሁሉም እኩል የሚሰራና ተፈፃሚ የሚሆን፥፥

በቃ ዋናው ነገር ህገመንግስቱን አትንካ ነው፥፥

አስታውሳለሁ በአንድ ወቅት የአለም መንግስታት ተባብረው ቢንላዲንን ለመደብደብ ብለው አፍጋኒስታንን በሚደበድቡበት ወቅት የኖርዎይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለተለያየ የስራ ጉዳይ በሚል በብዛት ወደ አፍጋኒስታን ይመላለሱ ነበርና እዛም ሲመላለሱ በአፍጋኒስታኖቹ ባህል ስጦታ የተለመሰ ነገር በመሆኑ ለካ አቶ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርዬ አንድ ምንጣፍ በስጦታ አጊንተው ሲመለሱ ስጦታው ወደድ ያለ ሆኖ እያለ ለኖርዌጂያን ግብር ስብሳቢ ቢሮ ወይንም /tax Administration/ ማስመዝገብ ሲገባቸው ዘንግተውት በኖርዎይ ትልቅ መነጋገሪያ ርእስ ሆኖ ሚዲያዎች ቁም ስቅላቸውን ሲያበሉአቸው ነበር፥ እንዲሁም ባንድ ወቅት የትራንስፖርት ሚኒስትርዋ በአንድ ወቅት አነስተኛ መርከብ ለመመረቅ ተጋብዘው በሄዱበት ወቅት ከአንድ ባለሃብት የእጅ ሰንሰለት የወርቅ በስጦታ አጊንተው እሳቸውም ዋጋው ውድ መሆኑን በለመረዳት ይመስላል ሳያስመዘግቡ በመቅረታቸው ሚዲያዎች ነገሩን ይደርሱበትና ካራገቡት በኋላ ታክስ አስቆርጠውባቸዋል ሚኒስቴርዋም ስጦታውን በመቀበላቸው እንደተፀፀቱ ለህዝባቸው ተናግረዋል፥፥

አሁን ግን ይህችን አጭር ፅሁፍ ለመፃፍ ያነሳሳኝ ከዚሁ ከኖርዎይ ሳልወጣ በዚህ በፈረንጆች ገና ዋዜማ በኖርዎይ ውስጥ ተሆነውን በሃገራችን ህልም ሳይሆን ቅዠት ወደሆነብኝ ነገር ልውሰዳችሁ፥፥

ከሶስት ወር በፊት በሴፕቴምበር 2013 በኖርዎይ በተደረገው የጠቅላይ ሚኒስቴር ምርጫ ተሸንፈው ስለጣናቸውን ያስረከቡት በኖርዎይ ምናልባትም ቁጥር አንድ ተወዳጅ ናቸው የሚባልላቸው የንስ ስቶልተንበርግ እንደውም ለምርጫው ጊዜ ታክሲ ሾፌር ሆነው ቅስቀሳ ሲያረጉ በነበረበት ጊዜ በኢሳት፥ በቢቢሲ የተዘገበላቸው http://ethsat.com/video/esat-kignet-taxi-shofieru-prime-minister/  የነበሩት ጠቅላይ ሚኒስቴር ለአሁኑ ገና በአል ዋዜማ ስራ ከለቀቁ በኋላ የመጀመርያ ስራቸው ያረጉት የገና ዛፍ መሸጥ ነበር፥፥

ዜናውን ሳየው ብዙም አልደነገጥኩም፥ ግን ቅናት አደረብኝ እንደውም ተስፋ ነው የቆረጥኩት፥፥

ሰውዬው እንዳልኩት በአንድ ወቅት በተለይ ኢኮኖሚ ክራይስስ ተብሎ አውሮፓውያኑ እየተጨናነቁ በነበረበት ወቅት ሃገራቸውን በብቃት ችግሩ ባጠገቧም ሳይደርስ ስላሳለፉት የሃገሪቷ ቁጥር አንድ ተወዳጅ ሰው ከንጉሱም በላይ ተብሎ ሚዲያ ላይ ወቶ እንደነበር አስታውሳለሁ፥ ሃብታም ናቸው፥ እውቀት አላቸው በነገራችን ላይ አባታቸውም የኖርዎይ ጠቅላይሚኒስቴር ሆነው አገልግለዋል፥፥ 

ብቻ ለማጠቃለል ያህል ሰዎቹ ከራሳቸው በላይ የሚያስቀድሙት ብዙ ነገር ዓላቸው፥ ህዝባቸው፥ ሃገራቸው፥ አላማቸው፥ ግባቸው፥ ሌላም ሌላም
እንግዲህ እስካሁን ስለ እነሱ ነው ያወራሁት ግን እኛስ

እኛ ማን ነን

ለምንድነው የምንታገለው

ለማን ነው የምንታገለው

ምንድነው አላማችንና ግባችን

ወደኛ ሲመጣ ይህ ጥያቄ ለሁላችን በግለሰብ ደረጃ መልስ ሊያገኝ የሚገባው ጥያቄ ይመስለኛል፥፥ 

ዝቅ እንበል

እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ

Saturday, November 30, 2013

"The Ethiopian Gov. Is Part Of The Problem" -Abebe Gellaw

Ethiopian Journalist, Abebe Gellaw joined SaharaTV’s Adeola Fayehun to explain the ongoing deportation of Ethiopians in Saudi Arabia. Gellaw, an exiled journalist and founder of Addis Voice stated that “There are over 30,000 Ethiopians held in concentration camps [in Saudi Arabia],” said Gellaw. He also noted that those in concentration camps rarely receive food and medical help. According to Gellaw, “The Ethiopian Government is part of the problem.” Because of oppressive living conditions in Ethiopia “The people of Ethiopia go to Saudi Arabia for better opportunities but unfortunately that hasn’t been the case,”said Gellaw. In efforts to expose this situation, Gellaw says he and other protestors are appealing to the international community.

Tuesday, November 19, 2013

[Must Watch Full Video] Who Will Forget These Ethiopians Voices From Sau...

በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ እየደረሰ ያለው መከራ፥ ስቃይ፥ እንግልት፥ ድብደባ፥ እስራት፥ ግድድያ፥ እና ስደት ገደቡን አልፏል፥፥ ይሁን እንጂ እኛ ኢትዮጵያውያን ይሄንን ሁሉ በደልእያየን እንዳላየን፥ በወገን ላይ በሚደርስ በደል ከንፈር ከመምጠጥ ያለፈ መንም አለመቆርቆራችንለምንድን ነው?

ሁላችንም እንኳን በወገን ላይ ለሚደርስ መከራ አደለም በራሳችንም ላይ ለሚደርስ መከራ ለበጎነው ብለን ከማለፍ ውጪ ፈቀቅ ያለ የተግባር ስራ ማረግ አለመቻላችን ከማሳዘን አልፎ አሳፋሪ ሰዎች እየሆንን መተናል፥፥

በተለይ በውጭ ሃገር የምንኖር ኢትዮጵያውያን በምንኖርባቸው አገራት ያለውን ለሰው ልጅ የሚሰጠውን ክብር እያየን፥ የሰው ልጅ የነፃነት መብት፥ የመናገር መብት እያየን እንኳን ይህ መብት ለኛ ለኢትዮጵያውያን እንደማይገባን ያህል ማሰባችን ያስገርማል፥፥

በቃ ህልማችን ሁሉ ውጭ ሃገር መተን የሰው አገር ባሪያ ሆኖ ለመቅረት የወሰንን ይመስላል፥፥ 

የሚገርመው ነገር ግን በአረብ ሃገር በኢውሮፕ እንዲሁም በአሜሪካም ጭምር ከሰው በታች ሆነን መኖራችን ነው፥፥

እንነሳ፥

እንነሳ፥

እንነሳ፥!

Sunday, November 10, 2013

SMNE Calls for Strong Measures from the International Community, Donors and International Investors in Confronting Official Corruption in Ethiopia

November 9, 2013
Press Release
Washington, DC, November 4, 2013

The Government of Ethiopia is broadly soliciting for development aid, foreign-based business partnerships and financial investors; yet, the unpopular ruling party has been accused of abuse of state power, misuse of donor funds, widespread party-run business monopolies, illicit financial practices and endemic corruption. It is time to demand accountability from all involved and concerned.

The Solidarity Movement for a New Ethiopia (SMNE) is a non-political and non-violent social justice movement of diverse people that advocates for freedom, justice, good governance and upholding the civil, human and economic rights of the people of Ethiopia, without regard to ethnicity, religion, political affiliation or other differences. The SMNE believes a more open, transparent and competitive market economy, supported by viable institutions and reasonable protections, which provides equal opportunity, will result in greater prosperity to the people rather than keeping it in the hands of a few political elites. 
We strongly contend that Ethiopia will not emerge as a dependable global economic partner until the corrupt and illegal practices of the current one-party regime’s monopoly end and existing blocks of entry to non-party members are lifted. We also believe the global business community as well as donors to Ethiopia can contribute by coming alongside Ethiopians in the push for meaningful reforms. Such reforms would include greater transparency and an opening up of economic space to the private sector, without which growth and development—beyond the benefit of the ruling party’s affiliates—will never be realized.
In light of this, the SMNE urges the international community, donor nations, charitable organizations, and the international financial and business community to make demands on the Government of Ethiopia (GOE) for compliance with national and international laws. This must include holding companies affiliated or owned by members of the ruling party, including those businesses associated with their business conglomerate, Endowment Fund for the Rehabilitation of Tigray, (EFFORT), accountable. Additionally, measures should also strongly support restoring autonomy to independent institutions, the judiciary, and the Media and upholding the human and economic rights of the people.
Until these measures are taken, the SMNE urges these stakeholders in the international community to withhold investments, development financing and other forms of partnering with the regime and its cronies.
The ruling TPLF/EPRDF party has misused its state power and expenditures of foreign aid to corner the market through its companies and affiliates in all sectors of the economy. Illegal expropriation of land and public resources, corruption, illicit capital leakage and dubious allegiances riddle these secretive deals, putting prospective partners at high risk for future liability or other uncertain consequences. 
The Oakland Institute in its July 17, 2013 press release: “Development Aid to Ethiopia: Overlooking Violence, Marginalization, and Political Repression,” warned the international community on the dangers of unwitting complicity in creating this illegal monopoly of business and civil society that provides the Ethiopian regime development aid amounting to “an average [of] $3.5 billion a year, equivalent to 50 to 60% of Ethiopia’s national budget.”
Likewise, the international community and investors have largely ignored or, knowingly or unknowingly, become complicit with the pervasive corrupt practices of many of the 100’s of companies owned and operated by theTigrayan Peoples’ Liberation Front (TPLF) that dominates the ruling coalition government of the Ethiopian Peoples’ Democratic Republic Front (EPDRF).“Companies under the Endowment Fund for the Rehabilitation of Tigray, known as EFFORT, alone account for roughly half of the country’s modern economy”, according to an IPS report titled “Examining the Depths of Ethiopia’s Corruption.” The wife of the late Prime Minister, Meles Zenawi, headed up the organization until only recently.
Bloomberg News, in its October 27, 2009 edition, reported Guna Trading House Plcowned by Ethiopia’s ruling party, said it plans to become one of the nation’s biggest coffee exporters, raising concern among industry observers that private industry may get crowded out.
The report quotes the late prime minister regarding the company’s plans to expand in the industry. ‘We are intending to export to Europe, the U.S. and China,’ he said. Guna is among at least four other companies owned by the state or Prime Minister Meles Zenawi’sruling party.”
Coffee Plantation Development Enterprise, Dinsho Trading P.L.C and Ambasel Trading House P.L.C. are among coffee exporters under the ownership of the ruling party that has been able to obtain favored treatment from public agencies and enterprises due to the regime’s control of these government agencies that should otherwise be holding them accountable. Companies that fall out of line can suddenly fall under the scrutiny of these agencies. As a result, those associated with the ruling party are able to dominate key industries, including the export of commodities. See some of the morevisible companies and less visible, like Wogagen Bank, Sheba Tannery P.L.C., Ambasel Trading House P.L.C., and many more companies owned by the ruling party.
Another company within EFFORT’s group is Almeda Textile Factory. According to the company, it is the biggest textile factory in Ethiopia. It is one of the major exporters of textile products to the US market. The company has had help in achieving this position through assistance from US government agencies, made available through the Africa Growth and Opportunity Act (AGOA). Additionally, according to the United States Agency for International Development‘s Newsthey report giving technical assistance to Almeda Textile Factory through the USAID East Africa Competitiveness and Trade Expansion Program (COMPETE). They also sponsored the company in an exhibit at the MAGIC Apparel Trade Show in August 2009.
Essentially, the US government agency admittedly supported this Ethiopian ruling party-owned company in its exports into the US market, also allowing Almeda AGOA’s duty free import privilege, something that was intended for independent businesses. This is in direct violation of US anti-corruption laws.
Another ruling party-owned company, Addis Pharmaceutical Factory, which dominates the local market, claims to be the largest pharmaceutical manufacturing plant in Ethiopia. According to the company, it manufactures “analgesics, anti-acids, antibiotics, anti-malarias, anti-asthmatics, amoebicides, anthelmenics, cough syrups and vitamin preparations.” Addis Pharmaceutical allegedly benefits from the expenditure of health funding from development agencies.  
The international community, including development agencies, charitable organizations and investors, often have ignored the implication of associating with the ruling party’s owned companies. This is contrary to the public interest and is in violation of international laws and regulations against corruption.
For example, in a press release on the appointment of the Bill and Melinda Gates Foundation’s first official representative in Ethiopia, the co-chair, Melinda Gates, said, “We invest more than half of our resources in Africa, and we want to build closer and more effective relationships with valued partners on the ground.”   
According to the Foundation, “Ethiopia is an important focus country for the foundation, which currently provides more than USD $265 million in funding to partner organizations that are operating health and development programs across the nation.” 
In Ethiopia, ruling party controlled organizations and businesses are nearly the only partners possible, creating an oligarchy similar to what has happened in Russia and other countries in Africa where totalitarian governments and their cronies pillage the economy and resources to their own advantage and without regard to the people.
What appears to be negligence and a lack of doing due diligence on the part of the foreign aid community and investors, including the UN Millennium Development Goal (MDG), the Bill and Melinda Gates Foundation, USAID, among many other agencies and investors, unfortunately contributes to making it possible for the ruling party and its affiliated companies to involve themselves in all kinds of shadow businesses while eroding the prospects for viable independent businesses to emerge and survive. 
As a result, in the last decade the number of parallel shadow business enterprises associated with the ruling party and affiliates have mushroomed in every sector of the economy while at the same time the international community has poured in billions of dollars in development aid and investment without appearing to question the ruling party’s extensive involvement in business and trade. 
Global Advice Network on its Business Anti-Corruption portal concludes in the profile on Ethiopia: “The [Ethiopian] government strategy is clearly top-down, dominating anti-corruption institutions, the anti-corruption debate, and the formulation of anti-corruption policy. Despite the introduction of anti-corruption initiatives in previous years, including the Federal Ethics and Anti-corruption Commission (FEACC) in 2001, corruption remains widespread at many levels of government administration in the country.”
In the findings of the Bertelsmann Foundation 2012 Report , they assert: “Ethiopian society’s deeply ingrained clientelism does not foster a culture of accountability and transparency, has fostered cover-ups and non-enforcement of laws”. For example, they report: “Competition laws aimed at preventing monopolistic structures and conduct exist within some sectors, but are enforced inconsistently. A Competition Commission was established in 2006, and by the end of 2007 had reviewed some 23 cases. Although informally provided, the strongest complaints are against the government’s preferences for party-affiliated businesses; [however], only trade-related issues were investigated. The transportation sector, for example, is to a large extent in the hands of business people belonging to the para-party sector. There are a number of companies close to the government and the ruling party, which leads to a lack of transparency and [high levels of] corruption.”  
A World Bank 2012 report on Ethiopia reinforces the same, saying that “high-level corruption is widespread within the construction sector, and that it is dominated by the ruling party affiliated companies.” 
Reports alone cannot fully capture the enormity of the ruling party’s affiliated companies’ extensive involvement in all sectors of the economy due to the ruling party’s control of:
  1. Public agencies such as: Ethiopian Rural Land Management Agency, Privatization Agency, Investment Commission, Commercial Bank of Ethiopia, Ethiopian Agriculture Transformation Agency, Ethiopian Grain Trade Enterprise, Development Bank of Ethiopia, The Federal Ethics and Corruption Commission, Information and Communication Technology Agency and others;
  2. Trade institutions such as: Chambers of Commerce and Sectoral Associations, The Ethiopian Commodity Exchange, Ethiopian Coffee Exporters Association and farmers and trade union and associations;
  3. Licensing and regulating of charitable organizations, which includes: The Ethiopian Charities & Civil Societies Agency (ECCA) and legislations severely limiting the kinds of activities—civic engagement important to healthy societies—that organizations are allowed to carry out if they receive more than 10% of their financing through foreign sources, rather than through government funding under the Charities and Societies Proclamation; resulting in the ruling regime’s operation of hundreds of charitable organizations, including the Tigray Development Association (TDA);
  4. Public Media infrastructures, including Ethiotelecom, (the only internet provider in the country) ‎ View shared postand Ethiopian Broadcasting Authority  (the only shortwave Radio and Television broadcasters in the country), The Ministry of Communication and Information Technology http://www.mcit.gov.et/
The UNDP commissioned Global Financial Integrity Report: ‘Illicit Financial Flows from the Least Developed Countries: 1990-2008’, revealed that approximately US$197 billion flowed out of the 48 poorest developing countries and into mainly developed countries, on a net basis over the period 1990-2008. Trade mispricing—when imports are overpriced and exports underpriced on custom documents—accounts for 65 percent of illicit financial flows.”
The report ranked Ethiopia among the top ten worst countries out of the forty-eight. As a recipient of the largest development aid in Sub-Sahara Africa, the international community has the obligation to hold the GOE and the ruling party owned business conglomerate and facilitating organization primarily responsible and accountable.
In light of these concerns, the SMNE calls on the international community, donor countries and organizations and financial institutions, investors or business partners, either prospective or established, to not ignore the overwhelming evidences of endemic corruption but to take strong measures to ameliorate the problem to the best of their ability through exposure, denial of services, investigations, criminal proceedings and remedial actions. Some of these actions should include:
  • Demand that the ruling party disclose and dissolve all its business holdings built on public resources and foreign aid
  • Demand that the ruling party affiliated charitable organizations’ including EFFORT Group, disclose their financial holdings to the public and cease operating charitable organizations
  • Call for an independent investigation of the regime’s business and charitable activities
  • Call for the immediate restoration of the independent Media, including allowing the international Media to operate freely in the country with full access to the public records
  • Demand public disclosure of all records on foreign investment, including land contracts for the purpose of commercial farming as well as real-estate, mining and manufacturing
The SMNE urges the international community, donor nations and organizations, Ethiopian political parties, civic and religious organizations and the Media, at home and abroad, to pressure the international communityto:
  • Not provide a blank check and diplomatic cover for the Government, the ruling party and its affiliated companies
  • Require meaningful conditions be met as part of receiving development aid and diplomatic support
  • Closely monitor the misuse of military and security assistance they or others have provided that has helped the ruling party gain control of the ways and means of the economy
  • Open an investigation on crimes of corruption and money laundering on the part of the ruling party’s affiliated companies, officials, and family members residing inside or outside of the country, in their respective jurisdictions abroad
  • Close any access for the ruling party affiliated companies that do business in the international markets until compliance with international and national laws are followed.
The SMNE and partners advise all concerned organizations to use established laws, agreements and protocols, where possible, to compel the ruling party to abide by international and regional conventions and protocols as well as to follow all applicable laws and regulations on corruption both nationally and internationally. 

Wednesday, November 6, 2013

TPDM TV AMHARIC interview with tegay mola asgedom chair man of TPDM 30-10-13 PART-1-

የወያኔ ሰራዊት እየተዳከመ ነው:: ( SEE VIDEO 3 PARTS )


የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ማለት የሃገራችን ኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ሳይሆን ያለው የስርኣቱ (የኢህኣዴግ) ሰራዊት ሁኖ ነው ያለው፣ የሃገር መከላከያ ሊሆን የሚችለው የኣገሩን ደንበር ጣባቂ ኣስከባሪ፤ የህዝቡን መብት ጠባቂ፤ ለህገ-መንግስቱ ተገዢና የኣንድ ፓርቲ ጥገኛ ያልሆነ ነው፣ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ግን የወያኔ ሰራዊት ነው፣ በሌላ ደግሞ ሰራዊቱ እየተዳከመ ነው፣

የመዳከሙ ውጤትም ወደ 2 ፤ 3 የሚጠጉ ክ/ጦሮች ወደ ሌላ ክ/ጦሮች ተበትንዋል፣ እኛ የምናውቋቸው ክ/ጦሮች እኳ 19ኛ፤ 35ኛ፤ 12ኛ የመሳሰሉ ክ/ጦሮች ኣሁን ወደ ሌላ ክ/ጦሮች ተበውዘዋል፣ የዚህ ምክንያት ደግሞ በጣም ብዙ የሚባሉ ከሻለቃ በላይ የነበሩ ኣመራሮች ከመከላከያ ተባርረዋል፣ ሌላው ምክንያት ደግሞ በመከላከያ ውስጥ መክዳት ብቻ ሳይሆን ትልቁ ነጥብ እርስ በርስ መተማመን የለም፣ በቅርብ ግዜ ራሳቸው ያጠፉ የሻለቃ ኣመራሮችም ኣሉ፣

ህወሓት ሊወድቅ የሚችለው የህዝብ ትግል ሲፋፋም ብቻ ነው፣ የህወሓት ኣመራሮች ቢሰናጠቁ ኣንዱ ተባርሮ ኣንዱ ታስሮ እንዲህ በንዲህ እያለ ህወሓት በደከመ ሁኔታ በስልጣን ይቆያል፣ ከስልጣን ለማስወገድ ዋነኛው ኣማራጭ ግን መታገል ነው፣


PART ONE http://www.youtube.com/watch?v=7rpDvX1nOg4
PART TWO http://www.youtube.com/watch?v=PIZ9QYBKPoA
PART THREE http://www.youtube.com/watch?v=H_tRnLUbRYo




Sunday, October 27, 2013

Nelson Mandela escaped assassination in Ethiopia


A Retired Ethiopian Police Officer, Commander Gudeta Dinka, Relates the Plot to Assassinate Nelson Mandela in Addis Ababa. 
Nelson Mandela is known to have taken military training in Ethiopia as part of a support he was getting for his Anti Apartheid struggle. Former Ethiopian Police Officer, Commander Gudeta Dinka, has said to the local radio station in Addis Ababa, Ethiopia, that once he was asked to kill the then military trainee, Nelson Mandela. 

Gudeta Dinka, 76, was a police officer under the command of General Tadesse (A top military officer, then colonel, who was appointed by the Emperor himself for the training and safety of Mandela). The retired officer told the radio station that it was only four people; General Tadesse, Colonel Fekadu, Commander Fekade and he were allowed to a tight section in the Kolfe Police Academy where Mandela stayed and took training. 

Mandela used to leave the window open at night; the commander remembers. He said that as he was one of those in charge of Mandela’s safety, once he was contacted by a police officer to discuss on a very serious matter. When they met at Taitu Hotel, Commander Guta relates that the officer gave him 2,000 pounds and offered him to strangle Mandela. 

The commander remarked that the officer offered a lot more money for both of them and a safe way out of the country if he killed Mandela.
“Finish him and when you leave the compound a car will be waiting for pickup. Two chances are before us. We shouldn’t miss them…” said the officer to commander Guta, as he remembered the incident. 

“I acted as if I have agreed, and then I told about the plot to General Tadesse. The plot held in great secrecy and those people behind the plot got identified and then banished from the country” said the retired police officer, Commander Guta Dinka.

Tuesday, October 15, 2013

Wikileaks Ethiopia Files; Ethiopia Bombs Itself, blames Eritrea, Oromos 2006, 2011?

By Thomas C. Mountain

Recently released Wikileaks Ethiopia files expose how Ethiopian security forces planted 3 bombs that went off in the Ethiopian capital Addis Ababa on September 16, 2006 and then blamed Eritrea and the Oromo resistance for the blasts in a case that raises serious questions about the claims made about the bombing attempt against the African Union summit earlier this year in Addis Ababa, Ethiopia.
In a report from 2006 marked “Secret ; Subject: Ethiopia: Recent Bombings Blamed on Oromos Possibly the Work of GOE [Government of Ethiopia]...by: Charge [d'Affairs] Vicki Huddleston”, “An embassy source, as well as clandestine reporting, suggests that the bombing may have in fact been the work of the GoE security forces.” Cable reference id: #06ADDISABABA2708
At the time the western media reported the Ethiopian National Intelligence and Security Service (NISS) claims that the bombs were “part of a coordinated terror attack by the OLF [Oromo Liberation Front, the oldest national liberation movement in Ethiopia] and Sha'abiya (Eritrea) aimed at disrupting democratic development”.
The Wikileaks report goes on, “a typically reliable information source), contacted Post to report that” the bodies of three men found at the bomb sites were “men [who] had been picked up by police a week prior, kept in detention and tortured. He said police then left the men in a house and detonated explosives nearby, killing 3 of them.”
This exposes the history of how the Ethiopian regime has planted bombs and then blamed Eritrea and the Ethiopian resistance. The lies that make up the official version of this alleged terrorist attack raises serious questions about the credibility of the recently released report by the UN via its US State Department affiliate, the Monitoring Group for Eritrea and Somalia which blames the Eritreans and the OLF for the January bombing attempt at the African Union summit in Addis Ababa, Ethiopia. Identical lies about a nearly identical “terrorist attack”, all accepted as fact by the western media. This should also deliver another body blow to the Obama White House and its claims that Eritrea supports terrorism in the Horn of Africa.
So once again the bellowing against Eritrea by the USA and it lackeys at the UN going back to 2006 is exposed as complete bunkum and an identical frame up of Eritrean and the Oromo resistance in Ethiopia that has been regurgitated by the UN and its truth challenged Monitoring Group on Eritrea and Somalia must be subject to a more critical scrutiny. Based on this expose' it can only be hoped that the UN inSecurity Council, which has yet to decide whether to pass severe sanctions against Eritrea, will refrain from doing so.
Thomas C. Mountain is the only independent western journalist in the Horn of Africa, living and reporting from Eritrea since 2006. He can be reached at thomascmountain at yahoo dot com.

Sunday, October 13, 2013

Sunday, October 6, 2013

ወያኔን ለማስወገድ አስገዳጅ የትግል ስልት ወሳኝ ነው!!!

ከለምለም አንዳርጌ(ኖርዌይ)

ላለፉት ሁለት አስርተ አመታት ኢትዮጲያና ሕዝቦ ላይ እንደ መዥገር ተጣብቆ ይህ ነው የማይባል ግፍና ሰቆቃ ሲፈጽም የኖረው የዘረኛው የወያኔ ስርዓት የእድሜ ዘመኑ ማብቂያ ጠርዝ ላይ ለመሆኑ ኢትዮጲያን ያህል ሃገርና ህዝብ ከሚመራ ስርዓት የማይጠበቁ የማፍያ ተግባራቱ ስርዓቱ ያለበት የዝቅጠት ደረጃ ጠቋሚዎች ናችው፡፡ በእድሜ ዘመን መጀመሪያ በስም እንጂ በተግባር ዴሞክራሲን የማያቀው የአንድ ጎጥ ቡድን ለይስሙላ ባስቀመጠው ህገ-መንግስት የተካተቱትን የዜጎችን መብት በመሻር ሃገሪቱን የምድር ሲኦል አርገዋታል፡፡ በሃገሪቱ ህገ-መንግስት መሰረት መብታቸውን አውቀው የተቋቋሙ የሞያ ማህበራትም ሆኑ የፖለቲካ ድርጅቶች በራሳቸውም ሆነ በስርዓቱ ተጽእኖ ይህ ነው የማይባል ተግባራት ሳይከውኑ በዘረኛው ስርዓት እየተኮረኮሙ ይፈርሳሉ አልይም በሞኖፖል በተያዘው የፍትህ ስርዓት ተወንጅለው በግፍ በእስር  ይማቅቃሉ፡፡
ከአመታት በኋላ ፍርሃታቸውን አሸንፈው የወያኔ መናጆ መሆን ይበቃናል ብለው ህገ-መንግስቱ የሚፈቅድላቸውን መብት ለመጠቀም ከዚህ በፊት ባልተለመደ መልኩ ወያኔን እምቢኝ እያሉ ያሉት በአገር ውስጥ በሰላማዊ መንገድ የሚታገሉት ጥቂት የፖለቲካ ድርጅቶች መብታቸውን ተጠቅመው የሚያደርጉት የሰላማዊ ትግል መርህ የዚህን ዘረኛ ስርዓት ማንነት ፍንትው አድርጎ ያሳየን አጋጣሚ ነው፡፡ ምንም እንኳን የኢትዮጲያ ሕዝብ ስለወያኔ ማንነትና ምንነት የጠለቅ ግንዛቤ ቢኖረውም በዚህ ደረጃ በወረደና በዘቀጠ ማፊያ ቡድን እንደምንመራ ማመን በእጅጉ ይክብዳል፡፡

አንድ የፖለቲካ ድርጅት እንደ ድርጅት ምልኡ የሚሆነው የተነሳለትን አላማና እቅድ እንዲሁም የሕዝብን መሰረታዊ የመብት ጥያቄዎች ተግባራዊ ምላሽ እንዲያገኙ በፅናት መታገል ሲችል ነው፡፡ እንደ ወያኔ ያለ አምባገነን ስርዓት አፍኖ ለያዘው የሕዝብ የመብት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጠው በተፅኖ እንጂ በችሮታ አይደለም፡፡ ለሚጠየቀው ህገ መንግስታዊ የሕዝብ ጥያቄ ተገቢውን ምላሽ እንዲሰጥ አይጠበቅም አምባገነን ነውና፡፡ ስለሆነም መብቱን የሚያስከብር  ለምን?! እን?! በቃኝ፣! እምቢ! የሚል የሕዝብ አደረጃጀት እንዲኖር የፖለቲካ ድርጅቶች በተገቢው ደረጃ ሕዝብን ማደራጀትና መርሆና፣ እቅዳቸውን ማስረፅ እንዲሁም ለለውጥ የተዘጋጀ ትግሉን ከዳር ሊያደርስ የሚችል ፍርሃቱን የሰበረ የህብረተሰብ ሃይል ሊገነቡ ግድ ይላቸዋል፡፡
ይህንን ህዝብ ለትግል በማነፅ የግፍ ቀንበሩን  ከጫንቃው ላይ ማውረድ የሕዝብ  ወገን ነን ከሚሉ የፖለቲካ ድርጅቶች የሚጠበቅ ተግባር ነው፡፡ የትኛውም የትግል ስልት አይነቱ ይለያይ እንጂ ቁርጠኝነትና መስዋትነት ይፈልጋል ስለዚህም አታጋዮቻችን መገንዘብ ያለባቸው የምንጠይቀው የሕዝብ መብት ወያኔ በችሮታ የሚሰጠን  የኛ ያልሆነ ሳይሆን ሰብአዊ ፍጡር በመሆናችን ልናገኝ የሚገባን እውነታችን እንደሆነ ሊገነዘቡ ይገባል፡፡ እናም ለእውነት ዋጋ ለመከፈል ዝግጁነት ያስፈልገናል፡፡ ትግሉ በከረረ ቁጥር ዘረኛው ስርዓት ማጣፊያ ሲያጥረው  ለሚወስደው ማንኛውም እርምጃ መቋቋም በሚያስችል መልኩ ጠንካራ አደረጃጀት ሊኖረን ግድ ይላል ፡፡

የወያኔ ዘረኛ ቡድን ህገ መንግስቱ የሚፈቅድልንን ለቁጥር የሚታክቱ መብቶቻችንን ቢነፍገንም፣ ሚያዚያ 30 1997ዓ.ም የነበረውን የቅንጅት የድጋፍ ሰልፍ ተከትሎ ለስምንት አመታት ቀምቶን የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ ህገ መንግስታዊ መብታችንን ለማስመለስ ከአመታት በሗላ  በወጣቶች ለተደራጀው ሰማያዊ ፓርቲ  ምስጋና ይግባውና እጅግ በተጠና ወቅትና ጊዜ የመሰለፍ መብታችንን ከገዢዎቻችን እጅ አውጥቶ በሕዝቡም የተጫነውን የፍርሃት ድባብ በመግፈፍ እረገድ  ሃላፊነቱን ተወቷል፡፡
ከዚህ አኳያ የረፈደ ቢመስልም በአሁኑ ወቅት በሃገር ውስጥ እየተከናወኑ ያሉ የሰላማዊ ትግል እንቅስቃሴዎች ለዘረኛው ቡድን የራስምታት መሆናቸው አያጠያይቅም፡፡
የሰማያዊ ፓርቲ ስኬት ለሌሎቹ እንደ ማንቂያ ደውል በመሆኑ አንድነት ፓርቲም የሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት በሚል መሪ ቃል በክልል ከተሞችና በአዲስ አበባ እጅግ ፈታኝና ከእልህ አስጨራሽ ትግል በኋላ የተሳካለት ሊባል የሚችል ሰላማዊ ሰልፍ አድርጓል፡፡

99.6 የሕዝብ ድምጽ አለኝ የሚለው የወያኔ ዘረኛ ቡድን በመልካም አስተዳደር ችግርና በኑሮ  ውድነት እንዲሁም በፍትህ መጓደል የተንገሸገሸውን ሕዝብ በመፍራት ሰልፉን ለማደናቀፍ የቻለውን ያህል ቢጥርም መሰዋትነት ለመክፈል በቆረጡ የድርጅቱ አመራርና ጠንካራ አባላት ጥረት የታሰበውን ሰላማዊ ሰልፍ ማስተጓጎል ሳይቻለው ቀርቷል፡፡
ይህ የሚያሳየው በነፃነት የመኖር ሰዋዊ መብታችንን በአፋኝ አምባገነን መሪዎች መነጠቃችን ነው፡፡ ስለሆነም መብታችንን ለማስመለስ(ለማስጠበቅ) አስገዳጅ የትግል ስልት እንደሚያስፈልገን አጠያያቂ አይደለም፡፡ በመሆኑም አሁን ያለውን የሕዝብ ለነጻነትና ለትግል የመነሳሳት መንፈስ በተጠናከረና በተደራጀ መልኩ ለማስቀጠል ቁርጠኛ እርምጃ መውሰድ ይጠበቅብናል፡፡ በዘረኞች ለሚፈበረኩና ነጻነት የሚነፍጉ ህግጋቶችን እምቢ አሻፈረኝ የሚል ህዝብ ለመፍጠር የድርጅት አመራሮች ከዚህ በተሻለ በቁርጠኝነት መስራት ይኖርባቸዋል፡፡
ድል ለኢትዮጲያ ሕዝብ!!!

Thursday, October 3, 2013

ይህ ትውልድ ለወያኔ ቀኑ ሲደርስ ፍም እሳት ነው!

ለስምንት አመታት በሐገራችን ምንም አይነት ተቃውሞ ሰልፎችን ማድረግ በገዢው መንግስት ተከልክሎ የነበረ ቢሆንም እገዳውን ሰብረው ህገ መንግስቱ በሚፈቅድላቸው መብት መሰረት ተጠቅመው ብሶታችንን ላሰሙልን ለጀግኖች ወገኖቻችን ይሆን ዘንድ ይህንን ምስል ማስታወሻ አዘጋጅቼዋለሁ።
እምቢ እምቢ እምቢ በል
ከእስክንድር ኖርዎይ

Sunday, September 29, 2013

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!

ኢትዮጵያዊ ታጋሽ እንጂ ፈሪ አደለም፥
ኢትዮጵያዊ ሁልግዜም ነፃነቱን ተቀብሎ እንጂ ሰቶ አያቅም፥፥

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!



Monday, September 9, 2013

የሐምሌ ጨረቃ! ከአንዱዓለም አራጌ ዋለ (አንድነት ም/ሊቀመንበር ከቃሊቲ ማጎሪያ) ክፍል አንድ

ከጉልበተኞች ጠመንጃ የሚወጣ ጥይት ስጋን እንጂ እምነትን ሊገድል እንደማይችለው ሁሉ፣ ከቤተሰብና ወዳጅ ዘመድ ተነጥሎ ቅዝቃዜ በዋጠው ጠባብ ክፍል ውስጥ መታሰርም አካልን እንጂ ምናብን (ህልምን) ሊያስር የሚችልበት ጉልበት የለውም፡፡ ከቶስ እንደምናብ ሜዳውን፣ ተራራውን፣ ቁልቁለቱን፣ ዳገቱን፣ ሸለቆውን፣ ኮረብታውን በሰከንድ ክፍልፋዮች ከብርሃን ፈጥኖ በመምዘግዘግ ያለመዛነፍ ያሰበበት የሚደርስ ምን ኃይል አለ? ከጠባቧ ክፍል ውስጥ ‹‹ድርሻህ›› ተብላ በተሰጠችኝ 90 ሴንቲ ሜትር ላይ ቀሪ ህይወቴን አሳልፍ ዘንድ በግፍ ፍርድ ብታሰርም ዕረፍት ለማያውቀው ምናቤ ገለታ ይድረሰውና ይዞኝ ይከንፋል፤ ወደ ምፈልገው አድርሶ ይመልሰኛል፡፡


አንዳንዴ ከጁፒተር ማዶ ያሉ ተንሳፋፊ ዓለማቶችን ቢያስቃኘኝም፣ አብዛኛውን ጊዜ ግን በሀገሬ ሰማይ ስር በጥቅጥቅ ደመና ላይ አንሳፎ ታላላቅ ወንዞቿን፣ ሃይቆቿን፣ የተንጣለሉ መስኮቿንና ሰማይ ጥግ የሚደርሱ ተራሮቿን በመንፈስ ያስጐበኘኛል፡፡ በተራሮቿ ግርጌና በመስኮቿ እምብርት ላይ ችምችም ብለው የተሰሩ ጐጆ ቤቶችንና በውስጣቸው ለሺ ዓመታት በፍቅር የኖሩ ደሃ ኢትዮጵያውያንን እንደጓደኞቻቸው ከሚመለከቷቸው የቤት እንስሳቶቻቸው ጋ ይታዩኛል፡፡ በየከተሞቹ ከድህነትና ከአፈና ጋር ግብግብ የገጠሙ፣ ከድህነትና ከፖለቲካ አፈና ነፃ ለማውጣት በዓለም ዙሪያ የተበተኑ ወገኖቼን ሳይቀር በአይነ- ህሊና ያስጎበኘኛል፡፡ አንዳንዴ ውሸትን እንደብልህነት፣ አፈናን እንደ አገዛዝ ስልት የወሰዱ አሳሪ ወንድሞቼና እህቶቼ የህሊና ጓዳ ውስጥ ይዞኝ ዘው ይልና ያረበበውን እብሪት፣ ፍርሃት፣ ጭንቀት፣ እርስ በእርስ የሚላተሙ ሃሳቦቻቸውን ፍልሚያ… ያሳየኛል፡፡
እነዚህ ምን አይነት ኢትዮጵያውያን? ምን አይነትስ ወላጆች ናቸው? ብዬ ራሴን እጠይቃለሁ፡፡ የምናብ ፈረስ ጋልቤ የምጐበኘው የዚህን ዘመን ክንዋኔ ብቻ ሳይሆን የተደራረበውን የዘመን ጉም እየጠራረጉ ያለፉ አያሌ ዘመናትን ወደ ኋላ አስጉዞ ያሳየኛል፡፡ የኢትዮጵያን የከፍታ ዘመናት፡- አክሱምን፣ ላሊበላን፣ ጐንደርን፣ ያልዘመርንለትን የገዳ ዴሞክራሲ ስርዓትንና ሌሎች የጥንት ስልጣኔዎችን በብላሽ ያስኮመኩመኛል፡፡ የኢትዮጵያን የዳር ድንበር ነፃነት ለማስከበር አባቶቻችን ያደረጓቸውን የጀግንነት ውሎዎች በተለይም የጀግንነታችን ማማና የጥቁር ህዝብ ሁሉ ኩራት የሆነውን የአድዋን ጦርነት ደጋግሜ አየዋለሁ፡፡ አድዋና መሰል የጀግንነት ማማዎች ላይ ቆሜ ኢትዮጵያውያን በየቀያቸውና በየዘመኑ ሰብዓዊ ክብራቸው ተረግጦ፣ በጭቆና አዘቅት ውስጥ ወድቀው ሲዘቅጡ ይታዩኛል፡፡ አንዳንዴ ኢትዮጵያውያን ሰብዓዊ ልዕልናቸውንና ነፃነታቸውን ለመጐናፀፍ ያደረጉትን ትግል ያሳየኝና መንፈሴን ያበረታዋል፡፡
ታሪክ እንደሚዘክረው ከኋላ ቀሩ የፊውዳል አገዛዝ ነፃ ለመውጣት (በትክክል ወዴት ያመራ እንደነበር መናገር ባይቻልም) የመጀመሪያ አብሪ ጥይት የተተኮሰችው የ1953ቱ የእነ ጄኔራል መንግስቱና ገርማሜ ንዋይን የመፈንቅለ-መንግስት ሙከራ በተደረገበት ዕለት ነው፤ አቤት! እርሱን ተከትሎ የተሻለ ንቃት ያለው ኢትዮጵያዊ በሙሉ ‹‹ሕዝባዊ መንግስት›› ለመመስረት ያሳየው እንቅስቃሴ! የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ለዓመታት የሞቱለት፣ የተጋዙለት፣ የተደበደቡለት፣ የተሰደዱለት… ሰላማዊ ትግል እና ያነሷቸው ጥያቄዎች ጆሮዬ ላይ ደጋግመው አስተጋብተዋል፡፡ በወቅቱ የዘውዳዊ ስርዓት ገበሬዎች፣ ተማሪዎች፣ ሰራተኞችና ልዩ ልዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ተቃውሞአቸውን በሰላማዊ መንገድ አሰምተው፣ በሰላም ወደ ቤታቸው እንዲገቡ የነበረውን ትዕግስት አሁን ካለው ሁኔታ ጋር ባነፃፀርኩት ቁጥር እንደ አዲስ እደመምበታለሁ፡፡ ንጉሳዊውን ስርዓት በመቃወም ተደጋጋሚ ሰልፎች ላይ ይሳተፉ የነበሩት እና ዛሬ ለድል የበቁት የቀድሞዎቹ ተማሪዎች፣ የአሁኖቹ ገዥዎች የትምህርት ነፃነትን ከመርገጣቸውም በላይ ቅሬታ በተነሳ ቁጥር የተማሪዎች መኝታ ቤት ድረስ በመዝለቅ ደም ማፍሰሳቸውን ሳስብ፤ ለተቃውሞ አደባባይ የሚወጡ ንፁሃን ላይ ከውሃ ይልቅ ጥይት ማዝነብ የሚቀናቸውና ተቃዋሚዎቻቸውን በውሸት ድሪቶ ዘብጥያ የሚያወርዱ አምባገነኖች መሆናቸውን ሳስብ የማይፈታ እንቆቅልሽ ይሆንብኛል፡፡
ዘውዳዊ ስርዓቱን የተቃወሙ ሰዎች ከነገስታቱ በላይ ከዘመን ጋር የማይዘምኑ፣ ከአፈሙዝ ጋር የተጋቡ እንዴት ሊሆኑ ቻሉ? የሚል ጥያቄ አነሳለሁ፡፡ የምናብ ፈረሴ ኢትዮጵያውያን ወደዚህ ዓለም በመጣሁበት ሰሞን ከነበረው የጭቆና አገዛዝ ነፃ ለመውጣት አልመው ወደ ከፋ የአምባገነንነት ገደል የወደቁበትን የእልቂትና የዋይታ አብዮት እየደጋገመ ያስቃኘኛል፡፡ በተፋላሚዎች መካከል የርዕዮተ-ዓለም ልዩነት ባይኖርም አፈ-ሙዝን በአፈ-ሙዝ ለማሸነፍ የተደረገው ደም መፋሰስና ወንድም በወንድሙ አስከሬን ላይ ቆሞ የፎከረበት የእርስ በርስ ጦርነትም ሌላኛው እረፍት የሚነሳው ጉዳይ ነው፡፡ ህወሓት/ኢህአዴግ የግፍ ቋት የነበረውን ደርግ በኢትዮጵያ ሕዝብ ድጋፍ አሸንፎ በድል አድራጊነት ወደ ምኒሊክ ቤተ-መንግስት ሲገባ ሌላ የግፍ ቋት ይሆናል ብለው ያልጠበቁ አያሌዎች ነበሩ፡፡ ረጅሙ የመከራ ሌሊት መልሶ ላይጨልም ነግቷል ብለው ለተሻለ ነገር የተዘጋጁ ኢትዮጵያውያን ቁጥር ትንሽ የሚባል አልነበረም፡፡ በአሁኑ አገዛዝ ከቀደሙት ህገ-መንግስታት የተሻለ ህገ-መንግስት ቢፀድቅም ቃልና ተግባር ሳይገናኙ ይኸው 22 ዓመታት አልፈዋል፡፡
እነሆም የሌላ ዙር የአፈና ሰለባ ሆኜ ወደምማቅቅበት እስር ቤት የምናቤ ፈረስ መልሶ አደረሰኝ፡፡ ሌላ ዙር እስር፣ ሌላ ዙር አፈና፣ ሌላ ዙር የህፃናት ለቅሶ፣ ሌላ ዙር የወላጆች ሰቆቃ፣ ሌላ ዙር ውርደት፣ ሌላ ዙር የአጤዎች ቀረርቶ፣ ሌላ ዙር የህዝብ እንባ፣ ሌላ ዙር… ባለንበት መርገጥ ቀጥለናል፡፡
የኢትዮጵያ ሕዝብ የከበረና ከፍ ያለ መስዋዕትነት በመክፈል የዳር ድንበር ነፃነቱን ማስከበር ቢችልም በአገሩ ሰብዓዊ ክብሩንና ነፃነቱን ከራሱ ገዢዎች አስከብሮ መኖር የቻለበት ዘመን የለም፡፡ አንዴ ሞቅ ሌላ ጊዜ ቀዝቀዝ እያለ የቀጠለው የኢትዮጵያ ህዝብ የነፃነት ትግል በድቅድቁና ዝናባማው የሐምሌ ጨለማ የምትወጣውን ‹‹ጨረቃ›› ይመስላል፡፡ በተለይ የኤሌክትሪክ ብርሃን በሌለበት የገጠሩ የሀገራችን ክፍል የልጅነቱን የመጀመሪያ ዓመታት እንደእኔ ላሳለፈና የኢትዮጵያን የፖለቲካ ትግል በአንክሮ ለተከታተለ ሁሉ ስርዓቱና ጨረቃዋ የአንድ አባት ልጆች ይሆኑበታል፡፡ የሐምሌ ወር ጨለማ ጥቁር ነው፡፡ እንደግድግዳ ፊት ለፊት ቆሞ ነፍስን ያስጨንቃል፡፡ ጫፉ የማይታይ የጥላሸት ቁልል ይመስላል፡፡ ከጨለማው መደቅደቅ የተነሳ በቅርብ እርቀት ያለ ቁስን እንኳን ለመለየት የሚያስችል ብርሃን የለም፡፡ ወደሰማይ ለሚያንጋጥጥም በጥቁር የደመና ከል የተጋረደ ነው፡፡ በዚህ መሃል ግን ህልቆ መሳፍርት ለሌላቸው ዘመናት የሐምሌ ወርን እየጠበቀች እየደጋገመች የምትወጣው ጨረቃም ወቅቷን ጠብቃ መውጣቷን አላቋረጠችም፡፡ ከአንድ ጥቁር የደመና ኮረብታ ወደሌላው ስትወረወር ለቅፅበት ትንሽ ብርሃን ብትፈነጥቅም ምድሩን እንደቡልኮ የሸፈነውን ድቅድቁን ጨለማ ሰንጥቆ ለማለፍ የሚችል የብርሃን ፍንጣቂ በመልቀቅ የጨለማውን ሀይል መግፈፍ የሚችል አቅም የላትም፡፡ እንዲያውም በብርሃን ጅረት የተሞላው መላ አካሏ በጨለማው ፅልመት ጠልሽቶና ከጨለማው ጋር ተመሳስሎ ይታያል፡፡ የሐምሌ ጨረቃ ወይ ድቅድቁን አትገፋ፣ ወይም የሐምሌን ወር አትዘል በየዘመኑ፣ በየአመቱ ፍሬ አልባ ዑደቷን ቀጥላለች፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ትግልም እንዲሁ፡፡ እንደ ሐምሌ ጨረቃ ሁሉ የኢትዮጵያ ሕዝብም የሀገሩን የህላዌ እድሜ ያህል ከጭቆናው ሌሊት ጋር በየወቅቱ ግብግብ ይገጥማል፡፡ በተለይም ከ1953 ዓ.ም ወዲህ ያሉት 50 ዓመታት ህዝባችን ከአብራኩ ከወጡ አምባገነን ገዥዎች መዳፍ ነፃ ለመውጣት ተደጋጋሚ ትግል አድርጓል፡ ፡ አሁንም እያደረገ ነው፡፡ ይሁን እንጂ የሰብዓዊ ልዕልናው ባለቤት ለመሆን የሚያስችለውን የተጠና፣ በከፍተኛ የኃላፊነት ስሜት የሚመራና ህዝብ የራሱ ያደረገው የፀና ሰላማዊ ትግል በማድረግ ለውጤት አልበቃም፡፡
ለምን? በረጅሙ የሀገራችን ታሪክ የሀገርን ዳር ድንበር ማስከበርን የመሳሰሉ ገንቢ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ፣ ፍልስፍናዎች ማዳበር የመቻላችንን ያህል፤ በሌላ መልኩም አሉታዊ የሆኑ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ስነ-ልቦናዊ ፍልስፍናዎች እንዳዳበርን መረዳት ይቻላል፡፡ እነዚህ ሁኔታዎች ፖለቲካዊ መስተጋብራችን የተፋለሰ እንዲሆን አስተዋፆ አድርገዋል፡፡ በተለይም ከዘመነ-መሳፍንት በኋላ ያለውና በዚያ ዘመን የፖለቲካ ብሒል የተቃኘው ፖለቲካዊ ፍልስፍናችን ከምህዋሩ የወጣ ነው፡፡ በአመዛኙ በፍርሃት፣ በአድርባይነትና በጊዜያዊ ጥቅም የተለወሰ ፍርሃት፣ የማያምኑበትን መናገር፣ በአርምሞ ማሳለፍ፣ ያልሆነውን ሁነን መታየት፣ ነገሮችን በሚስጥር መያዝ፣ ተጠራጣሪነትና በውል ባልታሸ ሁኔታ እራስን ማዕከል ያደረገ አስተሳሰብ ማራመድ የመሳሰሉትን ለአብነት ያህል ማንሳት ይቻላል፡፡ በየዘመኑ የሚነሱ አምባገነኖችና የጎበዝ አለቆች ጥላ ስር ለመጠለል መሞከር እነርሱን አይነኬ አድርጐ መቁጠር እራስን ፍፁም አቅመ-ቢስ አድርጐ መረዳት ለገዥዎች ማሸርገድና ቅዳሴ-ማህሌት መቆም አያሌ ኢትዮጵያውያን በየዘመኑ እንደ ፖለቲካ-ጥበብ የሚቆጥሩት አካሄድ ነው፡፡ ይህም ሁሉ በጥልቅ አስተሳሰብና ከዚያም በሚመነጭ እምነት ላይ ቢመሰረት ችግር አልነበረውም፡፡ የተሳሳተ እምነት በማንገብ የጨለማ አገዛዞችን የነፃነት ንጋት ናቸው ብለው የሚዘምሩ፤ በረሃብ ስንሞት በቁንጣን ነው ብለው ሊያሳምኑን የሚዳዳቸው፤ የአገዛዞች ዋልታና ማገር የሆኑ ኢትዮጵያውያንን በየዘመኑ አይተናል፡፡ እያየንም ነው፡፡
ከዘመናት የአፈና አገዛዝ ነፃ ልንወጣ ይገባናል ብለን የምንታገል ወገኖች እንደመኖራችን ሁሉ፤ አገዛዙ የፀሐይ መውጫ ምኩራብ ነው ብለው የሚያምኑ ወገኖች እምነታቸውን ያራምዱ ዘንድ መብታቸው ነው፡፡ ከስሜታዊነት በፀዳ መልኩ ጨለማው በእርግጥም ጨለማ መሆኑን አይኖቻቸውን ገልጠው እንዲያዩና እንዲመለሱ ማድረግ ይገባል፡፡ ሞታችን ከጨለማው ጋር ነው ብለው በጨለማው አካልነታቸው መቀጠል የሚፈልጉ ከሆነ ደግሞ ታግሎ ማሸነፍና እነርሱም ከጨለማ ነፃ እንዲወጡ ማድረግ ነው፡፡ ከባዱ የቤት ስራና እስከአሁንም ነፃነት ከእኛ እንዲርቅ ትልቁን አስተዋፆ እያበረከተ ያለው ከፍተኛ ቁጥር ያለው ‹‹መሃል ሰፋሪው›‹› ኢትዮጵያዊ ይመስለኛል፡፡ እውነቱን ለመናገር በፖለቲካ ትግል ባሳለፍኳቸው ጥቂት ዓመታት ከባዱ ፈተና የገጠመኝ ከቤተሰቤ፣ ከወዳጆቼና ከቅርብ ጓደኞቼ ነው ብል ማጋነን አይሆንም፡፡ እነዚህ ወገኖች ፖለቲካ ውስጥ ገብቼ ከአገዛዙ ጋር ግብግብ ከመግጠም ይልቅ አንገቴን ደፍቼ ልጆቼን እንዳሳድግ ምክራቸውን በተደጋጋሚ ለግሰውኛል፡ ፡ ለነገሩ ትዳር ባልያዝኩበት፣ ልጆች ባልነበሩኝ ወቅትም ‹‹አርፈህ ተቀመጥ!›› የሚለው ምክራቸው አልተለየኝም ነበር፡፡ ትግል ውስጥ እንዳልገባ የሚሰጡኝ ምክንያቶች ሁለት ናቸው፡፡ የሀገራችን ፖለቲካ በደም መፋሰስና በሸፍጥ የተሞላ መሆኑ አንደኛው ሲሆን በተጨማሪም ከኢኮኖሚ አዋጭነት አንፃር ፖለቲካ ፈፅሞ የማይመከር መሆኑን ያስረዱኛል፡፡ በመሆኑም አንገቴን ደፍቼ፣ ገዥዎች ወደአጋዙኝ ተግዤ እንድኖር፤ ልጆቼንም እንዳሳድግ ምክራቸውን ለግሰውኝ ነበር፡፡ አሁን እንኳን በእስር ላይ እያለሁ እንደሳይቤሪያ ብርድ አጥንትን ሰብሮ የሚገባና ነፍስን የሚወጋ ምክራቸውን ይልኩልኛል፡፡ ‹‹ነግረነው አልሰማንም››፣ ‹‹ህፃናት ልጆቹን ያለአባት ትቶ እንዴት ይታሰራል?›› ይላሉ፡፡ አንዳንዶቹ ከመበሳጨታቸው የተነሳ የመጐብኘት መብቴ ቢከበር እንኳን ሊጐበኙኝ እንደማይፈልጉ ይናገራሉ፡፡ ወንጀልሰርቼ እንዳልታሰርኩ፣ ለመስራትም እንደማላስብና ሰላማዊ የትግል ስልትን የሃይማኖት ያህል እንደማምንበት ወዳጆቼም ሆኑ አሳሪዎቼ እኔ የማውቀውን ያህል ያውቃሉ ብል ያጋነንኩ አይመስለኝም፡፡
ያም ሆኖ ግን ወዳጆቼ ስርየት እንደሌለው ሃጢያት፣ የአገዛዙ ዋናዎችም የሰማይስባሪ እንደሚያክል ወንጀል የቆጠሩት የተቃውሞ ፖለቲካ ጐራ መቀላቀሌን፣ በሀገሬ አንገቴን ቀና አድርጌ በመራመዴና የማምንበትን በቀጥታ በመናገሬ ነው፡፡ አገዛዙም ይኽን አይነት በፍርሃት የተሸበበ ማህበረሰብ እንዲፈጠር ይፈልጋል፤ ወዳጆቼም አገዛዙ በግፍ ስላሰረኝ የነቢይነት ደረጃቸውን በመደመምያስባሉ፤ እርስ በእርሳቸው ይመጋገባሉ፡፡ የትችት ጦራቸውን እስር ቤት ድረስ የሚወረውሩት አብዛኞቹ ጓደኞቼ በታላላቅ ዩኒቨርስቲዎች የተማሩና የሚያስተምሩ፣ በመደበኛ ትምህርት ልህቀታቸው በሊቀ- ጠበብትነት ጐራ የሚሰለፉና ይህች ደሀ አገር ከውስን ጥሪቷ ቆንጥራ ያስተማረቻቸው ናቸው፡፡ የሆነ ሆኖ ዛሬ ወዳጆቼ ያሉት ደርሶብኛል፤ ትንቢታቸው ሰምሯል፡፡ አዎ! ልጆቼ በድንገት ከቤት ወጥቶ እስከአሁን ወደቤት ስላልተመለሰው አባታቸው በህፃንነት የአእምሮ ጓዳቸው ውስጥ እያንሰላሰሉና እየተጐዱ መሆኑን በሚገባ እረዳለሁ፡፡ በተለይ ልክ የታሰርኩ እለት የትምህርት ቤትን ደጃፍ የረገጠው የልጄ የሩህ ጥያቄዎች ከዕለት ወደ ዕለት እየበረከቱ መጥተዋል፡፡ ‹‹ማሚ፣ እኔ አባት የለኝም እንዴ?››፣ ‹‹አባባ መቼ ነው ቤት የሚመጣው?››፣ ‹‹የአንተ ስራ መቼ ነው የሚያልቀው?›› የሚሉ ናፍቆት ያንገበገባቸውን ጥያቄዎች ያነሳል፡፡
እኔ የምከፍለው ዋጋ ይቅርና ልጆቼም በውል በማይረዱት ነገር ትልቅ ዋጋ እየከፈሉ መሆኑን በጥሞና እገነዘባለሁ፡፡ ቀድሞውንም ያልጠበኩትም አልነበረም የሆነው፡፡ ግና! በልጆቼ ሰብዕና ላይ የከፋ ስብራት እንዳይደርስ እውነተኛ ፈራጅ ወደሆነው ፈጣሪ ከመፀለይ በቀር ምን ማድረግ ይቻለኛል? ይህችን ምድር ለመጀመሪያ ጊዜ የተቀላቀለው በእስር ቤት ነው፤ ይኸው አሁን ደግሞ ባልጠኑ እግሮቹ፣ ክፉ ደግ ባለየ ህሊናው ከሚያፈቅረው አባቱ ተለይቶ በባዕድ ምድር የፖለቲካ ስደተኛ ሆኖ የሚንከራተተው የናፍቆት እስክንድር ነጋ ህይወት ለዚህ የበቃው አባቱ እንደኔ የወዳጆቹን የአርምሞ ጥያቄ ባለመቀበሉ ጭምር ነው፡፡ አባታቸውን ተመላልሰው መጠየቅ በማይችሉበት እርቀት ላይ የታሰረባቸው የናትናኤል መኮንን ልጆች እንባም ሰብዓዊ ፍጡርን በተለይም የወላጆችን ልብ ምንኛ እንደሚሰብር ግልፅ ነው፡፡ ከሚያስተምርበት አዲሰ አበባ ዩኒቨርስቲ፣ ከግቢ ውጭ እንደሚፈለግ በስልክ ሲነገረው የጠመኔውን ብናኝ ከእጁ ላይ አራግፎ የወጣው የኦሮሞ ፌዴራሊስ ኮንግረስ /ኦፌኮ/ ም/ሊቀመንበር በቀለ ገርባ ‹‹የኦነግ አባልና የፌደራላዊ አገዛዙን በኃይል ማስገንጠል አሲረሀል›› በሚል ክስ ተፈርዶበት ከህፃናት ልጆቹ ተለይቶ በዝዋይ እስር ቤት የግፉን ፅዋ እየተጎነጨ ነው፡፡ በእርግጥ አቶ በቀለም እንደ እኛ አርፎ ልጆቹን እንዲያሳድግ ተነግሮት ነበር፡፡ ሌሎች አያሌ ኢትዮጵያውያንና ልጆቻቸውም ተመሳሳይ የመከራ ህይወት እየገፋ ይገኛሉ፡፡ ልጆቻችንና የትዳር አጋሮቻችን እየከፈሉ ያሉት ዋጋ እኛ በእስር ቤት ከምንከፍለው የከፋ ይመስለኛል፡፡
ለጓደኞቼና ለወዳጆቼ የማነሳላቸው ጥያቄዎች ይኖሩኛል፡፡ ነፃነት አልቦ ህይወት ምን ምን ይላል? ለመሆኑ ነፃነትን በገዥዎች ችሮታ የተጐናፀፈው የየትኛው ሀገር ህዝብ ነው? በየትኛው ክ/ዘመን ይሆን? …አባቶቻችን ዳር ድንበራቸውን ለማስከበር ልጆቻቸውን፣ ሚስቶቻቸውንና ዘመድ አዝማዶቻቸውን ከኋላቸው ጥለው ወደ አድዋ መዝመታቸው ስህተት ነበር እያላችሁን ይሆን? ቴዎድሮስ በመቅደላ፣ ዮሐንስ በመተማ ለሀገር ክብር መውደቃቸው ትርጉም የለሽ ነበር ማለት ነው? ሌሎች አባቶቻችንስ በጉራ፣ በጉንደት፣ በማይጨው እና በአያሌ የጦር አውድማዎች ለሀገር ክብር እንደወጡ ሲቀሩ የሚናፍቋቸው ሚስቶችና የሚሳሱላቸው ህፃናት ልጆች ያልነበሯቸው ይመስሏችኋል? አሉላ አባ ነጋ እስከ እርጅና ዘመኑ ድረስ ለሀገሩ ዳር ድንበር አጥር ሆኖ ጣሊያንና ግብፅን በማስጨነቅ ዛሬ የምንኮፈስበትን ታሪክ ማጐናፀፉ ስህተት ነበር እያላችሁ ይሆን? የእነ በላይ ዘለቀ፣ የእነ አብዲሳ አጋ፣ የእነዘርአይ ደረሰ፣ የእነ ራስ ደስታ ዳምጠው፣ የእነ አቡነ ጴጥሮስና የሌሎችም ስመ-ጥር ጀግኖቻችን ውሎ በከንቱ ጀብደኝነትና ግብታዊነት የተሞላ ነበር ማለት ነው? እነዚህ ጀግኖች የሀገራቸውን ዳር ድንበር ክብር ለማስጠበቅ ከቀያቸው ርቀው ሲጓዙ ሞትን ከፊት ለፊታቸው እያዩት የቆሙለት እውነት አመዝኖባቸው እንደነበር ዘንግታችሁት ይሆን? አባቶቻችን በየተራራውና ኮረብታው ስለሀገር ክብር ባይቀበሩ ኖሮ የዛሬዋን ኢትዮጵያ ማግኘት የምንችል ይመስላችኋል? ወይስ የዳር ድንበር ነፃነት ከተከበረ፣ ዜጐች በጭቆና ቀንበር ቢማቅቁ ምንም ክፋት የለውም እያላችሁ ነው? ወይስ ጭቆና ከአብራካችን በወጡ ሰዎች እስከሆነ ድረስ እንደክብር ይቆጠራል እያላችሁ ነው? የሀገርን ዳር ድንበር ለማስከበር የተከፈለው ዋጋ ጠጋ ብለን ስናየው የህዝብን መሰረታዊ የሉዓላዊነት ጥያቄ እንደሚያነሳ ሳታችሁት? አባቶቻችን ለሀገር ነፃነት የከፈሉት ዋጋ ተገቢ አልነበረም ካላላችሁ በስተቀር ለዜጐች ሉዓላዊነትና ለዕውነተኛ ዴሞክራሲያዊ መንግስት መታገል ስህተት ሆኖ የሚገኘው በምን ቀመር ነው? በዩኒቨርስቲዎች ስለ- ሰብዓዊ ፍጡር ልዕልና የምትማሯቸውና የምታስተምሯቸው ትምህርቶች ‹ነፃነት›ን በተመለከተ ምን ነበር ያሏችሁ? ወይስ ዲሞክራሲና ነፃነት ለእኛ ሀገር አይሰራም እያላችሁ ነው? የጥቁር ህዝብ ኩራት የሆነውን የአድዋን ድል ያስመዘገቡ አባቶች ልጆች ሉዓላዊነታችን ከገዥዎቻችን መዳፍ ነጥቀን ማስከበር ካልቻልን ‹የእሳት ልጅ አመድ› መሆን አይመስላችሁም? ሌላው ቢቀር ኢትዮጵያ የቅኝ ግዛትን ቀንበር እንዲሰብሩ የረዳቻቸው የአፍሪካ አገሮች በዴሞክራሲ ጐዳና በርቀት ጥለውን ሲተሙ፤ የእኛ በጭቆና አረንቋ ውስጥ መዳከር እንዴት ቁጭት አይፈጥርባችሁም? ወይስ የእናንተ ድርሻ ትችትና ታዛቢነት ብቻ ነው? እነዚህ ከፍ ብዬ ያነሳኋቸው ጥያቄዎች ለምወዳቸው ጓደኞቼ ብቻ ሳይሆን ‹‹የመሃል-ሰፋሪነት›› ሚና ለመረጡ ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ ሁሉ የተሰነዘሩ ናቸው፡፡
ኢትዮጵያውያን በፖለቲካ ባህላችን ውስጥ ያሉ ሸንኮፎችን አስቀድመን መግረዝ ካልቻልን፤ የኢትዮጵያ ህዝብ ትግል እንደ ሐምሌዋ ጨረቃ አሁንም በከንቱ ብቅ ጥልቅ ከማለት የዘለለ ፋይዳ አይኖረውም፡ ፡ ምናልባት የሀሳባችሁ ማጠንጠኛ ባለፈው ግማሽ ምዕተ-ዓመት ማሳካት ያልተቻለው እንዴት አሁን ይቻላል? የሚል ከሆነ ይኸንን ጥያቄ ማንሳት፣ ለጥያቄውም መልስ መስጠትና በመልሱም ላይ ተመስርቶ በእውነተኛ ነፃነትና ህዝባዊ ልዕልና ላይ የተመሰረተች ኢትዮጵያን ለመፍጠር መታገል እንደሚያስፈልግ መተማመን ላይ መድረስ ይጠበቅብናል፡፡ የተወሰኑ ጥያቄዎችን አክዬ ላንሣ፡ ፡ ሁሉም የግል ጥቅሙንና የአብራኩን ክፋዮች ብቻ በሚያስቡባት ሀገር እንዴት ህዝብ ከአገዛዝ ነፃ ሊሆን ይችላል? በየማጀቱ አገዛዙን በመርገም ነፃ መውጣት ቢቻል ኑሮ ከረጅም ዘመናት በፊት ነፃ አንወጣም ነበር ትላላችሁ? አባቶቻችን ለነፃነት መስዋዕት መሆናቸው ትክክል ነበር የምትሉ ከሆነ የስብዕና መሰረትና የነፃነቶች ሁሉ የበላይ ለሆነው የሰብዓዊ መብት መታገል ትክክል የማይሆንበት አሳማኝ ምክንያት ምንድን ነው? ከገዥዎች መዳፍ ለመውጣት አሳማኝ ምክንያት ምን ሊሆን ይችላል? ይኽን ከገዥዎች መዳፍ ለመውጣት የሚደረግን ትግል እንዳላየን አይተን ብናልፍ ለሁላችንም የማይቀረው ሞትን ተጋፍጠን ወደመቃብር ስንወርድ በምን አይነት ክብርና የህሊና እረፍት ማሸለብ እንችል ይሆን? የዘወትር ህልማችን ሰብዓዊ ልዕልናችን ተጠብቆ የምንኖርበትንና ልጆቻችን የማያፍሩበትን ሀገር ማውረስ ሆኖ ሳለ የአገዛዙን የጭቆና አርጩሜ በመፍራት ከእምነታችን ውጭ የሆኑ ተግባሮችን ስንፈፅም የምንበጀው እስከመቼ ነው? ለዘመናት እላያችን ላይ ቤት የሰራብንን የጭቆና ቀንበር መስበር በረጅሙ የኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ያልተከወነ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲንከባለል የመጣ የቤት ስራ ነው፡፡ በውዝፍ ያደረ ቁምነገር ከቅርሶቻችን ሁሉ የገዘፈና የታሪካችን ፈርጥና የማንነታችንም መደምደሚያ ነው፡፡ በዚህ የሰብዓዊ ልዕልና ጉዳይ ላይ መታገል ሰው የመሆንና ያለመሆንን ጥያቄ መመለስ ነው፡፡ በነፃነት አለመታገል የቤት ስራውን ለልጆቻችን ወዝፎ ማሳደር በጭቆና ቀንበር ለመገዛት ህዝበ ውሳኔ የመስጠት ያህል ይቆጠራል፡፡ በሌላ በኩል ነፃ ለመውጣት እንደቀድሞ ነፃ አውጭ አበጋዞችን መጠበቅ አይገባንም፡፡ ይኽን የምናደርግ ከሆነ ሰማያችን በጭቆና ደመና እንደተሸፈነ ይቀጥላል፡፡ ጥቂቶችን አንጋጠን ስንጠብቅ በውስጣችን ያለውን ትልቅ የነፃነት ሃይል እንዳናይ ግርዶሽ ይሆንብናል፡፡
ይኽን በመሰለው የነፃነት ትግል የሚጀምረው የራስን የከረመና የተሳሳተ ፖለቲካዊና ማህበራዊ አስተሳሰብ ከመሞገት ነው፡፡ ከዚያም ከፍ ሲል እንደ ፖለቲካ ባህልና የብልህነት ቁንጮ በመውሰድ ለህፃናት ልጆቻችን ሳይቀር በምክር መልክ የምንለግሳቸው ልዩ ልዩ ያልተሰለቀቁ አሉታዊ አስተሳሰቦችን በቅድሚያ ታግሎ መጣል ያስፈልጋል፡፡ እያንዳንዱ ስለሁሉም ፤ሁሉም ስለእያንዳንዱ ግድ በማይሰጠው ሀገር ውስጥ አምባገነኖች የሚዘውሯቸው አገዛዞች መኖራቸው የግድ ነው፡፡ በዚህ ዘመን ስለነፃነት ክብርነት ለማንም ማስረዳት እምብዛም አይጠበቅብንም፡፡ ነፃነት እንደ እንጉዳይ በየዛፉ ስር ያለትልቅ መስዋዕትነት በቅሎ የሚገኝ አይደለም፡፡ ይኸንን የነፃነትን ውድነት ስንረዳ የሀገርን ዳር ድንበር ለማስከበር እንደዘመቱት አባቶቻችን ሁሉ ያለነፃነት ከመኖር ይልቅ ህፃናት ልጆቻችን ጥለን፣ ከሞቀ ቤታችን ወጥተን በእስር ቤት የሲሚንቶ ወለል ላይ መጣልን እንመርጣለን፡፡ በነገራችን ላይ ደጋግሜ ከምጠቅሳቸው ጀግኖች ጋር እራሴን እያወዳደርኩ አለመሆኑን አንባቢዎች ልብ እንድትሉልኝ እወዳለሁ፡፡ በታሪክ ኮረብቶች ላይ ከድንቅ የጀግንነት ውሎዎቻቸው ጋር ከፍ ብለው የሚታዩ ጀግኖች ጫፍ የሚደርስ አንዳች ስራ እንዳልሰራሁ ጥሩ አድርጌ እገነዘባለሁ፡፡ አላማዬ የዳር ድንበርን ሉዓላዊነት ከሰብዓዊ ሉዓላዊነት ጋር ማነፃፀር ነው፡፡
ሌላው የአገር ውስጥ ገዥዎችንን እንዴት ከውጭ ሀገር ወራዎች ጋር ያነፃፅራል? የሚል ጥያቄ ሊነሳ ይችላል፡፡ ሁለቱም የዘመቱት በነፃነታችንና ሰብዓዊ ክብራችን ላይ ነው፡፡ የነፃነት ትርጉም ከሀገር ልጅነትም በላይ ነው፡፡ በሰላማዊ ትግል መንገድ ስንጓዝ ትግላችን ጨቋኝ ወንድሞቻችን ወደልባቸው እንዲመለሱና ሁላችንም በነፃነት የምንኖርባትን የጋራ ሀገር እውን እንድትሆን ከማድረግ ጋር ነው፡፡ ከዚህ በዘለለ እንዲታመሙና እንዲሞቱ አይደለም ፡፡ በእኛና በልጆቻችን ላይ እያደረሱት ያለው በደል በእነርሱም ላይ እንዲደርስ ፈፅሞ የምንመኘው ነገር አይደለም፡፡ ነ ፃነትን ከውጭ ሀገር ወራሪም ሆነ ከሀገር ውስጥ ጨቋኝ መጠበቅ መቼም በይደር የሚያዝ ተግባር አይደለም፡፡ ስለሁላችን ነፃነትና ሉዓላዊነት የተዘረጋ የተማፅኖ ቃል እንጂ፡፡ በሀሰት ‹‹አሸባሪ›› ተብለን ዘብጥያ ብንወርድም ትግሉን ከመቀጠል ውጭ ሌላ አማራጭ የለም፡፡ ነፃነትን መጠየቅና መታገል ነፃነቱን የተጠማ የነፃነት ታጋይ ሁሉ ድርሻ መሆን ይኖርበታል፤ ይሁንና የናፈቃችኋትን ነፃነት አታገኟትም ብለው ወህኒ መወርወር የአፋኞች የአፈና ተግባር ቢሆንም መንበርከክ ለከፋ መከራ፣ ለበረታ ጭቆና ከማገለጥ ውጪ ትርፍ አልባ ነው፡፡ የአሁኖቹ ገዥዎች እንደ ቀድሞዎቹ ሁሉ የተሳሳተ የፖለቲካ ባህላችን ያበቀላቸው መሆኑን መረዳት ይገባል፡፡ የፖለቲካ ባህላችንና አስተሳሰባችን ካልተቀየረ እንደ እስከ አሁኑ ሁሉ ሌሎች አምባገነኖችንም ማብቀሉን ይቀጥላል፡፡
በአምስት አመት ውስጥ ማዕከላዊ እስር ቤት ሁለት ጊዜ ስታሰር፤ ሃላፊዎች ተለዋውጠው ባገኛቸውም የሁለቱም ዋና ኃላፊዎች ቃልና ተግባር ግን ትንሽ እንኳ ልዩነት አልነበረውም፡፡ በሚገርም ሁኔታ ሁለቱም እንዳገኙኝ የጠየቁኝ አንድ አይነት ጥያቄ ነበር፡፡ ‹‹ወንድ ከሆንክ ለምን ጫካ አትገባም?›› የሚል፡፡ ወንድነት ማለት አፈ-ሙዝን፤ በማይናወጥ የፍቅርና የወንድማማችነት መንገድ መጋፈጥ፤ ተጋፍጦም ሳይገሉ መሞት ነው ወይንስ በራሳችን ጥላ ሳይቀር እየደነበርን ንፁሃንን መግደል? የሚገርመው እኮ ለአፈ-ሙዝ ፍልሚያ የጥሪ ካርድ የሚበትኑት ወገኖች የደሃ ኢትዮጵያውያን ወንድማማቾችን ደም ለማፍሰስ እንጂ እነርሱማ ከመኪና ተደግፈው ለመውረድ ምንም የማይቀራቸው ናቸው፡፡ አንዳንድ በተለይም የአገዛዙ ዋነኛ ሰዎች ይችን ሀገር ለሁላችን ወደሚበጅ ንጋት ይዘዋት ለመውጣት እድሉን ለዓመታት ቢያገኙም ሊጠቀሙበት አልቻሉም፡፡ ይልቅስ እብሪት የሁለንተናቸው ማጠንጠኛ ምህዋር ሆኖአል፡፡ አንዳንዶቹን በጨረፍታ በማየት ለወንድማማችነትና የኢትዮጵያን የባጁ ችግሮች ለመፍታት በጐ አስተዋፆ ሊያደርጉ ይችሉ ይሆናል፣ ሕዝብን እንኳን ባይፈሩ ፈጣሪን ይፈሩ ይሆናል ብለን ተስፋ ብናደርግም ሁለቱንም እንደማይፈሩና የኢህአዴግ ዋና ሰዎች መለያ የሆነውን እብሪትና ሃኬት የሙጥኝ ብለው መንጐድ ቀጥለዋል፡፡
በኢትዮጵያ ታሪክ አገዛዞች ከዚህ የተለየ ሲያደርጉ አልታዩም፡፡ ይኸኛው አገዛዝ ከቀድሞዎቹ ለመለየት የሚሞክረው በእውነት ላይ ያልተመሰረተ የፕሮፓጋንዳ ደመራ በማቀጣጠል ነው፡፡ የፕሮፓጋንዳ ደመራው ህዝቡንም ሆነ አገዛዙን በብርሃን እንዲመላለስ አላደረገውም፡፡ ሊያደርገውም አይችልም፡፡ አገዛዙም ሆነ ህዝቡ ከፍርሃትና ከጨለማ ጉዞ ነፃ ሊወጣ የሚችለው የእውነት ችቦ ለኩሶ ከዚያም በሚገኘው ብርሃን ዙሪያ ተሰባስቦ መወያየት ሲቻል ነው፡፡ ለዜጐች ሉዓላዊነት ክብር የሚሰጥ አገዛዝ ቢኖር የፕሮፓጋንዳ ደመራ አቀጣጥሎ በዙሪያው መጨፈር ባላስፈለገ ነበር፡፡ ምክንያቱም ተግባር ከቃላት በላይ ይናገራልና፡፡ የአገዛዙን አምባገነናዊ ባህሪዎችና ተግባሮች በመተንተን ከዚህ በላይ ጊዜ ልናጠፋ አይገባንም፡፡ ምንስ የማይታወቅ ነገር አለ? እንኳን የአፈናው ሰለባዎች ኢትዮጵያውያን ቀርቶ ዓለምም በቅጡ ተረድቶታል፡፡ አገዛዙ ለህዝብ ፈቃድ የሚገዛ ቢሆን ለመቃወም ከቤታችን መውጣት ባላስፈለገን ነበር፡፡
ትልቁ መፈተሽ ያለበት ጉዳይ ከ50 ዓመታት በላይ የአገዛዝ ስርዓትን ከኢትዮጵያ የፖለቲካ ምህዋር ለማስወገድ የተደረገው ጥረት፣ የተከፈለው የህይወትና የአካል መስዋዕትነት እንዴት እስካሁን ለፍሬ ሊበቃ አልቻለም? የሚለው ነው፡፡ የተቃዋሚ ፓርቲዎች እስከ አሁን ቢያንስ ወደተሻለ ምዕራፍ ትግሉን ለማሸጋገር አልቻሉም? እስከ አሁን በተደራጁ የፖለቲካ ትግል ውስጥ ገብቶ ከመታገል ይልቅ በተለየና የራሳችን በሆነ መንገድ አስተዋፆ እናበረክታለን ብለን በተለያየ መስክ ተሰልፈን የምንገኝ ሰዎችም ምን ያህል አስተዋፆ አበረከትን? ብለን ራሳችንን መፈተሽ ይገባናል፡፡ ጊዜው በተግባር የማይደገፍና የተጠጋገኑ ምክንያቶችን በመደርደር ብቻ ከተጠያቂነት የምናመልጥበት አይደለም፡፡ ኢትዮጵያውያን የአፈናው ሰለባዎች መሆናችንን አለም በቅጡ ተረድቶታል፡፡ አገዛዙ ለህዝብ ፈቃድ የሚገዛ፣ የህግ የበላይነትን የሚያከበር ቢሆን ኖሮ ለመቃወም ከቤታችን መውጣት ባላስፈለገን ነበር፡፡ ትልቁ መፈተሽ ያለበት ጉዳይ ከ50 ዓመታት በላይ የአገዛዝ ስርዓትን ከኢትዮጵያ የፖለቲካ ምህዋር ለማስወገድ የተደረገው ጥረት፣ የተከፈለው የህይወትና የአካል መስዋዕትነት ዛሬም ለፍሬ ሊበቃ ያልቻለበትን ምክንያት ነው፡፡ የተቃዋሚ ፓርቲዎችስ ስለምን ትግሉን ወደተሻለ ምዕራፍ ማሸገር ተሳናቸው? ዛሬም ድረስ የተደራጀ የፖለቲካ ትግልን ተቀላቅሎ ከመታገል ይልቅ በተለየና የራሳችን በሆነ መንገድ አስተዋፆ እናበረክታለን ብለን በተለያየ መስክ ተሰልፈን የምንገኝ ሰዎችም አበርክቶአችን ምን ያህል እንደሆነ ራሳችንን መፈተሽ ይገባናል፡፡ ጊዜው በተግባር የማይደገፍና የተጠጋገኑ ምክንያቶችን በመደርደር ብቻ ከተጠያቂነት የምናመልጥበት አይደለም፡፡ የነፃነት ጉዳይ ‹ለነገ…› ተብሎ በይደር የሚቆይ አይደለም፡፡