Thursday, December 26, 2013

እኛና እነሱ /ዝቅ በል/ !

በአለም ላይ ካሉ ሃገሮች ውስጥ ስልጣን የሌለበት ሃገር ቢኖር ወይም ባለስልጣኑ ህዝብ የሆነበት ሃገር ቢኖር ሳላጋንን ኖርዎይ የምትባለው ሃገር ናት ማለት እችላለሁ፥፥ በግልፅ ህዝቡ የሚፈልገውን፥ ያስተዳድረኝ እገዛለታለሁ ብሎ አምኖ ድምፁን የሚሰጥለት መሪ፥፥ መሪውም ከልቡ እራሱን ዝቅ አርጎ ለሃገሩ፥ ለወገኑ የሚሰራበት ሃገር፥፣ ህገመንግስቱ ወይም በኖርዌጅያኑ አጠራር /GrunnLov/ ለሁሉም እኩል የሚሰራና ተፈፃሚ የሚሆን፥፥

በቃ ዋናው ነገር ህገመንግስቱን አትንካ ነው፥፥

አስታውሳለሁ በአንድ ወቅት የአለም መንግስታት ተባብረው ቢንላዲንን ለመደብደብ ብለው አፍጋኒስታንን በሚደበድቡበት ወቅት የኖርዎይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለተለያየ የስራ ጉዳይ በሚል በብዛት ወደ አፍጋኒስታን ይመላለሱ ነበርና እዛም ሲመላለሱ በአፍጋኒስታኖቹ ባህል ስጦታ የተለመሰ ነገር በመሆኑ ለካ አቶ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርዬ አንድ ምንጣፍ በስጦታ አጊንተው ሲመለሱ ስጦታው ወደድ ያለ ሆኖ እያለ ለኖርዌጂያን ግብር ስብሳቢ ቢሮ ወይንም /tax Administration/ ማስመዝገብ ሲገባቸው ዘንግተውት በኖርዎይ ትልቅ መነጋገሪያ ርእስ ሆኖ ሚዲያዎች ቁም ስቅላቸውን ሲያበሉአቸው ነበር፥ እንዲሁም ባንድ ወቅት የትራንስፖርት ሚኒስትርዋ በአንድ ወቅት አነስተኛ መርከብ ለመመረቅ ተጋብዘው በሄዱበት ወቅት ከአንድ ባለሃብት የእጅ ሰንሰለት የወርቅ በስጦታ አጊንተው እሳቸውም ዋጋው ውድ መሆኑን በለመረዳት ይመስላል ሳያስመዘግቡ በመቅረታቸው ሚዲያዎች ነገሩን ይደርሱበትና ካራገቡት በኋላ ታክስ አስቆርጠውባቸዋል ሚኒስቴርዋም ስጦታውን በመቀበላቸው እንደተፀፀቱ ለህዝባቸው ተናግረዋል፥፥

አሁን ግን ይህችን አጭር ፅሁፍ ለመፃፍ ያነሳሳኝ ከዚሁ ከኖርዎይ ሳልወጣ በዚህ በፈረንጆች ገና ዋዜማ በኖርዎይ ውስጥ ተሆነውን በሃገራችን ህልም ሳይሆን ቅዠት ወደሆነብኝ ነገር ልውሰዳችሁ፥፥

ከሶስት ወር በፊት በሴፕቴምበር 2013 በኖርዎይ በተደረገው የጠቅላይ ሚኒስቴር ምርጫ ተሸንፈው ስለጣናቸውን ያስረከቡት በኖርዎይ ምናልባትም ቁጥር አንድ ተወዳጅ ናቸው የሚባልላቸው የንስ ስቶልተንበርግ እንደውም ለምርጫው ጊዜ ታክሲ ሾፌር ሆነው ቅስቀሳ ሲያረጉ በነበረበት ጊዜ በኢሳት፥ በቢቢሲ የተዘገበላቸው http://ethsat.com/video/esat-kignet-taxi-shofieru-prime-minister/  የነበሩት ጠቅላይ ሚኒስቴር ለአሁኑ ገና በአል ዋዜማ ስራ ከለቀቁ በኋላ የመጀመርያ ስራቸው ያረጉት የገና ዛፍ መሸጥ ነበር፥፥

ዜናውን ሳየው ብዙም አልደነገጥኩም፥ ግን ቅናት አደረብኝ እንደውም ተስፋ ነው የቆረጥኩት፥፥

ሰውዬው እንዳልኩት በአንድ ወቅት በተለይ ኢኮኖሚ ክራይስስ ተብሎ አውሮፓውያኑ እየተጨናነቁ በነበረበት ወቅት ሃገራቸውን በብቃት ችግሩ ባጠገቧም ሳይደርስ ስላሳለፉት የሃገሪቷ ቁጥር አንድ ተወዳጅ ሰው ከንጉሱም በላይ ተብሎ ሚዲያ ላይ ወቶ እንደነበር አስታውሳለሁ፥ ሃብታም ናቸው፥ እውቀት አላቸው በነገራችን ላይ አባታቸውም የኖርዎይ ጠቅላይሚኒስቴር ሆነው አገልግለዋል፥፥ 

ብቻ ለማጠቃለል ያህል ሰዎቹ ከራሳቸው በላይ የሚያስቀድሙት ብዙ ነገር ዓላቸው፥ ህዝባቸው፥ ሃገራቸው፥ አላማቸው፥ ግባቸው፥ ሌላም ሌላም
እንግዲህ እስካሁን ስለ እነሱ ነው ያወራሁት ግን እኛስ

እኛ ማን ነን

ለምንድነው የምንታገለው

ለማን ነው የምንታገለው

ምንድነው አላማችንና ግባችን

ወደኛ ሲመጣ ይህ ጥያቄ ለሁላችን በግለሰብ ደረጃ መልስ ሊያገኝ የሚገባው ጥያቄ ይመስለኛል፥፥ 

ዝቅ እንበል

እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ